|
ማኅበረ ቅዱሳን
|
|
ትምህርተ ሃይማኖት
በትራክት መልክ የተዘጋጀውን የአማርኛ የጥምቀት መልእክት እዚህ ያግኙ 
Find the English Epiphany message in a tract form here 
የጥምቀት አስፈላጊነት
በቀሲስ ብርሃኑ ጎበና
በአራተኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከኒቂያ ጉባኤ በኋላ ከተነሱት አባቶች አንዱ “በፊተኛው ትንሣኤ ዕድል ያለው ብፁዕና ቅዱስ ነው ሁለተኛው ሞት በእነርሱ ላይ ሥልጣን የለውም” ራእይ ፳፥፮ የሚለውን የወንጌላዊው ዮሐንስን አባባል በተረጎመበት የእግዚአብሔር ከተማ በሚለው መጽሐፉ ላይ ፊተኛው ትንሣኤ የተባለው ሀብተ ወልድና ስመ ክርስትና የምናገኝበት ጥምቀት እንደሆነ ገልጿል (De Civitate Dei,xx,6)።
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ትምህርተ ሃይማኖት
በሊቀ ካህናት ኃይለሥላሴ ዓለማየሁ ደስታ
እግዚአብሔር ፈጣሪ ነው።
ፈጣሪ ስንል የሌለን ወይም ያልነበረን ነገር በሥልጣኑና በከሃሊነቱ ያስገኘ፣ ዓለምን እምሀበአልቦ /ካለመኖር ወደ መኖር/ የፈጠረ ማለታችን ነው። ዓለምን እምሀበአልቦ ያስገኘ፣ በመለኮታዊ ሥልጣኑ የሚታየውንና የማይታየውን፣ ግዙፉንና ረቂቁን ፍጥረት ሁሉ የፈጠረ እግዚአብሔር ነው።
እግዚአብሔር ዓለምን /ፍጥረቱን/ ለመፍጠር ምክንያት የሆነው መለኮታዊ ሥልጣኑ ብቻ ነው፤ የፍጥረታት ሁሉ አስገኝ እግዚአብሔር በመሆኑም የፍጥረታት ሁሉ ጌታና ባለቤት እግዚአብሔር ነው። እግዚአብሔር ዓለምን ፈጥሮ እንዲሁ አልተወውም፤ በመግቦቱ ይጠብቀዋል፤ ይህን ዓለም ካለመኖር ወደ መኖር ያመጣ እግዚአብሔር ብቻ በመሆኑና በመለኮታዊ ሥልጣኑ መሳይ ተወዳዳሪ ስለሌለውም እግዚአብሔር አንድ አምላክ ይባላል።
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ማኅበረ ቅዱሳን
“ስብሐት ለእግዚአብሔር በሰማያት ወሰላም በምድር ስምረቱ ለሰብእ”
ልደተ ክርስቶስን ስናከብር ከላይ የተጠቀሰውን የመላእክት መዝሙር እናስታውሳለን:: ቅዱሳን መላእክት ይህን ሰላምና እርቅን የሚያበስር መዝሙር ለመጀመሪያ ጊዜ የተቀኙት ለ5500 ዓመታት ጸንቶ የቆየው የጥል እና የመለያየት ዘመን ተፈጽሞ የእርቅና የአንድነት ዘመን መጀመሩን ለማወጅ ነው:: በአዳም በደል ምክንያት ለዘመናት ተለያይተው የነበሩት የሰው ልጆች እና ቅዱሳን መላእክት በጌታ ልደት ምክንያት ይህን መዝሙር አብረው ለመዘመር ቻሉ:: ሁላችንም የቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ልጆችም በያለንበት ሆነን በዓለ ልደቱን ስናከብር ይህንን መዝሙር በድምቀት እንዘምራለን::
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
ስብከተ ወንጌል
በመላከ ሕይወት ቀሲስ ዕርገተቃል ይልማ
ትራክቱን ለማግኘት ይህን ይጫኑ 
ቤተልሔም ማለት የእንጀራ ቤት ማለት ነው። ታሪካዊ ሥፍራ ናት። ዳዊትም ተወልዶ ያደገው፣ ለንጉሥነት የተቀባውና ቤተ መንግሥቱም የነበረው በቤተልሔም ነበር። ስለዚህ በእስራኤላዊያን ታሪክ ውስጥ ቤተልሔም የተወለደ «ቤተልሔማዊ ነኝ» ብሎ ራስን ማስተዋወቅ ክብር ነበረው። ቤተልሔም የእስራኤል መንግሥት ለሁለት ሲከፈል ቀድሞ የነበራት ታላቅነትና ዝና እንዳልነበረ ሆኗል። ከነቢያት ወገን የሆነው ሚክያስ ለማስተማር ሲያልፍ ይቺ ስመ ጥር የሆነችው ከተማ ተፈትታ፣ ምድረ በዳ ሆና፣ ቋያ በቅሎባት ክብሯ ሁሉ ከላይዋ ላይ ተገፎ ተመለከታት። ከተማይቱ እንደዚህ ሆና እንደማትቀር በመንፈስ ቅዱስ ተረድቶ «አንቺ ቤተልሔም ኤፍራታ ሆይ የይሁዳ ምድር፣ ከይሁዳ ገዥዎች ከቶ አታንሽም ሕዝቤን እስራኤልን የሚጠብቅ መስፍን ከአንቺ ይወጣልና» ሚክ ፭፥፪ ሲል ተነበየላት።
ተጨማሪ ያንብቡ
|
|
|